ይህ መልዕክት በዮሐ. 12፥37-43 ባለው ክፍል ላይ “የእግዚአብሔርን ክብር ማየት” በሚል ርዕስ በፎር ኮርነርስ ቤተክርስቲያን የተሰጠ ነው። ክፍሉ አይሁዳውያንና አለቆቻቸው ምንም እንኳ ኢየሱስ ክርስቶስ አሳማኝ ምልክቶችን በፊታቸው ቢያደርግ ያላመኑበትን ምክንያት የሚያሰረዳ ሲሆን ምልክት ምን እንደ ሆነ፣ ማመን ምን እንደ ሆነ በዝርዝር ይተነትናል። በክፍሉ ውስጥ የተጠቀሱትን ሦስት የነቢዩ ኢሳያስ ክፍሎች በማዛመድ ኢሳያስ በምዕራፍ 53 ላይ ያየው የመከራ ሰው በምዕራፍ 6 ላይ በክብር ዙፋን ላይ ያየው የእስራኤል ቅዱስ መሆኑን ያሳይና የእግዚአብሔርን ክብር በሁለት በመክፈል የሰው ምላሽ ምን ሊሆን እንደሚገባው በግልጽ ያብራራል።
Evangelist Yared Tilahun
www.goldenoil.org