ቅድስት እንባ መሪና
በዘመነ ጻድቃን በምድረ ግብጽ የተወለደች::
ከአባቷ ጋር መንና ወደ ወንዶች ገዳም የገባች::
ወንድ መስላ የወንዶችን ቀኖና በምንኩስና የተቀበለች::
ያለ አበሳዋ ወንድ መስላቸው ዝሙት ሰርተሻል ተብላ ወደ በርሃ የተባረረች::
ያልወለደችውን ልጅ ያሳደገች::
ያለ ምግብና ውሃ ለ3 ዓመታት የተሰቃየች::
ብርድና ፀሐይ የተፈራረቀባትና:
ስታርፍ ክብሯ የተገለጠላት ቡርክት እናት ናት::
ታሕሳስ 8 ልደቷ ነው፡፡
በረከቷ ይደርብን አምላከ ቅድስት እንባ መሪና ይቅር ይበለን፡፡ አሜን፡፡
ጻድቃን ጮሁ:: እግዚአብሔርም ሰማቸው::
ከመከራቸውም ሁሉ አዳናቸው::
እግዚአብሔር ልባቸው ለተሰበረ ቅርብ ነው::
መንፈሳቸው የተሰበረውንም ያድናቸዋል::
የጻድቃን መከራቸው ብዙ ነው::
እግዚአብሔርም ከሁሉ ያድናቸዋል::
እግዚአብሔር አጥንቶቻቸውን ሁሉ ይጠብቃል:: መዝ. 33:17
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ከዲን ዮርዳኖስ ፅሁፍ የተወሰደ
ይህን መንፈሳዊ ፊልም ተርጉመው ላቀረቡልን አጋፔ መንፈሳዊ መዝሙር ቤት እግዚአብሔር ይስጥልን::
ክፍል አንድ (1) የማይሰራላችሁ ከሆነ ይህን ሊንከ ነክታችሁ ክፍል አንድን ማየት ትችላላችሁ (በድጋሜ አፐሎድ የተደረገ ነው) https://youtu.be/rMwUheNjWpk